የግንባታው ዘርፍ ዋነኛ ችግር ሙስና እና አሳሪ የህግ ማዕቀፍ ነው ያለው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ነው።
ይህ የተነሳው ናሽናል ኮንስትራክሽን ሚዲያ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መስፍን ነገዎየዓለም ኢኮኖሚ ፎረም በፈረንጆቹ 2019 ባስጠናው ጥናት በአውሮፓ 46 በመቶ የግንባታው ዘርፍ በሙስና የተበላሸ መሆኑን አረጋግጧል ብለዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም በኢትዮጵያም የተደረገ ጥናት ባይኖርም ለሙስና ተጋላጭነቱ ከአውሮፓውያንየባሰ እንጅ የተሻለ አይህንም ሲሉ ለጣቢያችን ተናግረዋል።
ሌላው የዘርፋ ችግር የህግ ማዕቀፍ መሆኑን ባለስልጣኑ አንስቷል።
ዘርፉን ተንተርሰው የሚወጡ የህግ ማዕቀፎች ለሥራ የተመቹ ሳይሆኑ ከልካይ እና አሳሪ ናቸው ሲልየኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን አስታውቋል።
በተጨማሪም የግንባታ ዘርፉን የሚደግፉ የህግ ማእቀፎች ተካተው ስለማይፀድቁ በተፈለገው ልክ እድገት እንዳይመዘገብ አድርጎታልነው ያሉት ዳይሬክተሩ።
