የመሬት ልማትና አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 63 በመቶ ያህሉን ማሳካት አልቻለም

Date:

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ ካቀደው አጠቃላይ የገቢ ግብ ውስጥ 63 በመቶ የሚሆነውን ማሳካት እንዳልቻለ አስታወቀ፡፡

ቢሮው በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረው 45 ቢሊየን ብር ቢሆንም፣ መሰብሰብ የቻለው 16.6 ቢሊየን ብር (36.89 በመቶ) ብቻ በመሆኑ 28.4 ቢሊየን ብር ሳይሰበሰብ ቀርቷል፡፡

ቢሮው ሰኔ 14/2018 በከፍተኛ አመራሮቹ ባካሄደው የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ እንደገለጸው፣ በበጀት ዓመቱ የገቢ አሰባሰብን ጨምሮ ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመዘገበባቸውን ተግባራት ለማካካስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡

በዚህም መሠረት የተመዘገበውን ዝቅተኛ አፈፃፀም ለማካካስና የቀረውን የገቢ ግብ ለማሳካት የሚያስችል፣ በአመራሩ ልዩ ክትትልና ድጋፍ የሚመራ የዘጠና ቀን እቅድ ተነድፎ ወደ ተግባር ተገብቷል፡፡

ይህ እስከ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆየው የዘጠና ቀናት የማካካሻ እቅድ፤ ከመሬት ሊዝ ጨረታ፣ ከአገልግሎት ለውጥ፣ ከመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት፣ እንዲሁም በምደባ ከሚተላለፉ ቦታዎች የሚገኝ የሊዝ ቅድመ ክፍያን ጨምሮ ከተለያዩ የገቢ አማራጮች ከ17.34 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...

አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ...

ኢትዮጵያ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት ቀጣናዊ የሥልጠና ማዕከላት ሆና ተሰየመች

🔊 ስያሜው ኢትዮጵያን የቀጣናው የዕውቀት፣ የክህሎት ልማት እና የፈጠራ...