በመላው መካከለኛ ምሥራቅ እየተካhደ ያለው ጦርነት የሚያደርሰው ጉዳት እና ኪሳራ በሊባኖስ፣ በኢራን እና በዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ መታየት ጀምሯል።
በበርካታ የመካከለኛው ምሥራቅው አገራት በረራዎች ተቋርጠዋል። መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው የሰብዓዊ መብቶች አክቲቪስቶች የዜና ወኪል ጦርነቱ ከተጀመረ እስከ ሰኞ ዕለት ድረስ ብቻ ኢራን ውስጥ 1000 ሰላማዊ ዜጎች ሲገደሉ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሞቶች ደግሞ ሳይመዘገቡ መቅረታቸውን ገልጿል።




