የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት (KRF Norway) ከተሰኘው አጋር ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው “የፖለቲካ ተሳትፎ መመሪያ መፅሐፍ” ተመረቀ ።
የመመሪያው መፅሐፍ የኢትዮጵያ ፖለቲካን ለማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎለታል።
በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ መፅሐፉ ከምርጫ ሂደቱ ጋር ተያይዞ ልዩ ግብአት፣ ተሞክሮ እና አሰራሮችን የያዘ በመሆኑ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰሎሞን አየለ መፅሐፉን በርካታ ፋይዳዎች እንዳሉት ተናግረዋል።
የምረቃ ፕሮግራሙ አካል የሆነ የፓናል ውይይት በጉዳዩ ዙሪያም ተካሂዷል። ተሳታፊዎች ይህ መመሪያ መፅሐፍ ከዚህ ቀደም በተደራጀ መልኩ ያልነበረ በመሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ አካታች፣ ሰላማዊ እና የሰለጠነ የፖለቲካ ተሳትፎን ለማበረታታት ትልቅ ግብአት እንደሚሆን ነግረውናል።
መፅሐፉ በሰባት ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን የፖርቲዎች አመራር፣ የፖሊስ ቀረጻ ኮሙኒኬሽን የሚዲያ አጠቃቀም አካታችነት የጋራ ምክር ቤቶች ተሳትፎን አካቷል።
(አራዳ ኤፍ ኤም)
