የ2018 የድህረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና  ምዝገባ ይካሄዳል

Date:

በ2018 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ከመስከረም 20 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት አመልካቾች የመመዝገቢያ ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በማሟላት በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ እንደሚችሉ የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ገልጿል።

አመልካቾች ከምዝገባ ጋር ተያይዞ ለሚኖራቸው ጥያቄ ዘወትር በሥራ ሰዓት በ0920157474 ወይም 0911335683 እንዲሁም በኢሜይል አድራሻ ngat@ethernet.edu.et በኩል ማብራሪያ መጠየቅ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ሁሉም አመልካቾች የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ሊኖራቸው እንደሚገባም ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በተጨማሪም አመልካቾች የምዝገባ እና የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር በቴሌብር (TeleBirr) በኩል ብቻ መከፈል እንደሚኖርባቸው ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...