የ325 ሚሊዮን ዶላር ጉቦ የተቀበሉት የቻይና ባለሥልጣን ሞት ተፈረደባቸው

Date:

በምሥራቃዊ ቻይና የሚገኝ ፍርድ ቤት በ30 ዓመት ጊዜ ውስጥ 2.2 ቢሊዮን ዩዋን በላይ ወይም 325 ሚሊዮን ዶላር በሙስና በመቀበል የተከሰሱት የቀድሞ የከተማዋ አስተዳደር ባለሥልጣን ላይ የሞት ፍርድ አስተላለፈ።

ቅጣቱ የተላለፈባቸው ያንግ ዩሊን ከአውሮፓውያኑ 1993 እስከ 2023 ድረስ ባሉት ዓመታት ውስጥ በናንጂንግ ከተማ በተለያዩ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።

የቀድሞው ባለሥልጣን በማጭበርበር፣ ሥልጣንን አላግባብ በመጠቀም እና ሕጋዊ ያልሆነ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀሎች ተከስሰዋል። በእነዚህ ድርጊቶች አግኝተዋል የተባለው የገንዘብ መጠን በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቀረቡ ክሶች ያልታየ ነው።

የ69 ዓመቱ የቀድሞ ባለሥልጣን ኃላፊነታቸውን ተጠቅመው ሌሎች የኢንጂነሪንግ ውሎችን፣ የመሬት ባለቤትነት ዝውውር እና ገንዘብ እንዲያገኙ ማድረጋቸው ተገልጿል። ለዚህም በምላሹ ገንዘብ እና ቁሶችን መቀበላቸውን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።

ያንግ ምርመራ የተከፈተባቸው፤ ፕሬዝዳንት ዢ ሺፒንግ በከፈቱት የፀረ ሙስና ዘመቻ ነው። ይህ ዘመቻ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች፣ ትልቅ ባንኮች እና ሌሎች ዘርፎችንም ነክቷል።

ዢ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በተለያዩ ጊዜያት የፀረ ሙስና ዘመቻዎችን ከፍተዋል። ይሁን እንጂ እነዚህ ዘመቻዎች የፖለቲካ ተቀናቃኞችን ለማጥቃት ውለዋል የሚል ክስ ይቀርብባቸዋል።

ቻይና ውስጥ ለእንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች የሞት ቅጣት ማስተለላፈው የተለመደ አይደለም። ክሱ ከአንድ ቢሊዮን ዩዋን በላይ ወንጀል የተፈጸመበት ሲሆን ግን የሞት ቅጣት የተሰጠባቸው አጋጣሚዎች አሉ።

በ10 ዓመት ጊዜ ውስጥ 1.1 ቢሊዮን ዩዋን በሙስና ተቀብለዋል የተባሉ አንድ ባለሥልጣን 2021 ላይ በሞት ተቀጥተዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...