በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ መሆኑን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡
የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ እንደገለጹት፤ በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው፡፡
የአገሪቱ አንደኛ ደረጃ የሚባሉ ማዕድናትን ፍለጋ ላይ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በጉጂ፣ ቦረና፣ ከፊል ሶማሌ፣ ሱማሊያና ኬንያ ድንበር እና ሰቆጣ አካባቢ ያለው የብረት ክምችት ጥናት እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አካባቢዎቹ ሊቲየም፣ ታንታለም፣ ኒኬል፣ ማንጋኒዝ የሚባሉ ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት ነው፡፡
በውስን አቅም ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ላይ የምርመራ ሥራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ የአገር ፍላጎትን መሰረት በማድረግ በቅደም ተከተል በመሰራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ጋዜጣ ፕላስ
