ደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ዓለም የሚፈልጋቸው ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው

Date:

በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ መሆኑን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡

የማዕድን  ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ እንደገለጹት፤ በደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ያሉ አካባቢዎች አሁን ዓለም የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት አካባቢ ነው፡፡

የአገሪቱ አንደኛ ደረጃ የሚባሉ ማዕድናትን ፍለጋ ላይ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በጉጂ፣ ቦረና፣ ከፊል ሶማሌ፣ ሱማሊያና ኬንያ ድንበር እና ሰቆጣ አካባቢ ያለው የብረት ክምችት ጥናት እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡

እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አካባቢዎቹ ሊቲየም፣ ታንታለም፣ ኒኬል፣ ማንጋኒዝ የሚባሉ ዋና ዋና ማዕድናት ያሉበት ነው፡፡

በውስን አቅም ቢሆንም በእነዚህ አካባቢዎች ላይ የምርመራ ሥራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ የአገር ፍላጎትን መሰረት በማድረግ በቅደም ተከተል በመሰራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ጋዜጣ ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...