ዲያስፓራ አዳባባይ መገናኛ አካባቢ የደረሰ አደጋ

Date:


ዲያስፓራ አዳባባይ መገናኛ አካባቢ በደረሰዉ የተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳሰበ፡፡


በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የየካ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጋሻ ሁነኝ ሙሉጌታ እንደተናገሩት አደጋዉ 10፡30 አካባቢ በዲያስፓራ አዳባባይ በታክሲ ተርሚናሉ አካባቢ የደረሰ ሲሆን በአደጋዉ ሁለት ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዉ በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡


በታክሲ ተርሚናሉ ዉስጥ በተለምዶ ቅጥቅጥ የሚባለዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ወደ ኋላ ሲያሽከረክር ወድቆ ተንጠልጥሎ እንደሚገኝ ጨምረዉ ገልጸዋል፡፡


ተሽከርካሪዉ በአሁኑ ወቅት ከላይኛዉ ትሚናል ወደ ታችኛዉ ተርሚናል ተንጠልጥሎ ይገኛል፡፡


የእሳትና አደጋ መከላከል አሽከርካሪዎች በቦታዉ ደርሰዉ ተሽከርካሪዉን ለማንሳት ጥረት እያደረጉ መሆኑን የገለጹት ሃላፊዉ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ክትትል እየተደረገ ይገኛል፡፡


ከቀበና መጥተዉ ወደ ኮተቤ የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች በሚናሮል ጀርባ በኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ባለዉ አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙ አሳስበዋል፡፡


የትራፊክ ፖሊሶች በአካባቢዉ የትራፊክ እንቅስቃሴዉን በማሳላጥ ላይ እንደሚገኙም የየካ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጋሻ ሁነኝ ሙሉጌታ ተናግረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...