በፓኪስታን በባሉቺስታን አቧራማና በረሃማ በሆነ መሬት ላይ ባኖ ቢቢ የምትባል ሴት በታጠቁ ሰዎች —የጎሳዋ አባላት —ፊት ለፊት ኩራትዋን እና አለመሸነፏን አሳይታ ቆመች።
ከመገደልዋ ጥቂት ቀደም ብሎ፣ አሁን በሀገሪቱ ህዝቦች ህሊና ውስጥ ዘልቆ በገባው በቫይራል ቪዲዮ ላይ እንደታየው፣ ከጎንዋ ካለው ሰው ጋር በህጋዊ መንገድ መጋባትዋን ተናገረች።
ይህ የመጨረሻ የጀግንነት ተግባር ነበር። በቆራጥነት የተናገረችው ቃል በጥይት ምላሽ አገኘ።
ይህ የፊልም ትዕይንት አልነበረም። እውነት ነበር። አሰቃቂ። እና ሴቶችን ለመጉዳት “ክብር” የሚለው ቃል ለረጅም ጊዜ ሲያገለግል በቆየባት ሀገር ውስጥ በአሳዛኝ ሁኔታ የተለመደ ነገር ነው።
ባኖ እና ባለቤትዋ አህሳን ኡላህ የጎሳቸውን ፍቃድ ሳያገኙ በመጋባታቸው ተከሰው ነበር። አሁን በቫይራል በሆነው ቀረጻ ላይ ባህላዊ ቀይ ልብስ ለብሳ ብቻዋን ቆማ ስትታይ፣ አንድ የሰዎች ቡድን ደግሞ ባለቤትዋን ከበውት ይታያል። በአስፈሪ ቅዝቃዜ ባልና ሚስቱ የተገደሉት በወንጀል ሳይሆን ለፍቅር ሲሉ ነበር።
የጎሳ ሽማግሌዎች ጅርጋ የተባለውን ባህላዊ ምክር ቤት አቋቁመው፣ ቤተሰቦቻቸውን በመቃወማቸው በጥንዶቹ ላይ ሞት እንዲፈረድባቸው አዋጅ አወጡ ተብሏል። ይህ ፍትህ አልነበረም። በባህል ስም የተከናወነ የአምልኮ ግድያ ነበር።
ሰፊ ተቃውሞ ከተነሳ በኋላ የባሉቺስታን መንግስት ፈጣን እርምጃ ወሰደ። በወረቀት ላይ ቢሆንም። ባለሥልጣናት 11 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ያዋሉ ሲሆን፣ አንዳንዶቹም በግድያው በቀጥታ የተሳተፉ ሲሆን፣ ዘጠኝ ሌሎች ደግሞ አሁንም በነጻነት ይንቀሳቀሳሉ። የመጀመሪያ መረጃ ሪፖርት ተመዝግቦ ክስ ለመመስረት ቃል ተገብቷል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ከፊደል ፓስት
