ጎተራ አካባቢ ሊፈርስ መሆኑ ተሰማ

Date:


በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኘውና ጎተራ ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ሊፈርስ መሆኑን ዘሪፖርተር እንግሊዘኛ ጋዜጣ ትናንት ባቀረበው ዘገባ አስታውቋል፡፡

‹‹አዲስ ቱሞሮው›› በሚል ፕሮጀክት የከተማው አስተዳደር ለሚያስገነባው ልዩ የኢኮኖሚ መንደር አካባቢውን ለማፍረስ መታቀዱንም አስረድቷል፡፡

ፕሮጀክቱ በአዲስ አበባ ከንነቲባ አዳነች አቤቤና በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የሚመራ እንደሆነ የጠቀሰው ዘገባው የከተማው አስተዳደር መንደሩን ለመገንባት ከቻይናው የኮሚኒኬሽንና ኮንትራክሽን ድርጅት ጋር ስምምነት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡

መንደሩ የንግድ፣ የፋይናንስ፣ የትምህርት፣ የባህልና ሰማይ ጠቀስ የመኖሪያ ህንፃዎች እንደሚኖሩት መገለፁን ያስረዳው ዘገባው በመሆኑም በጎተራ አካባቢ በሚገኝ ሰፊ መሬት ላይ ለመስራት እንደታሰበ ጠቅሷል፡፡

የአዲስ ቱሞሮው መንደር ግንባታ በቢሊዮን የሚቆጠር ብር እንደሚፈጅ አስረድቶም ከዚህም በላይ በጎተራ አካባቢ የሚኖሩ በርካቶችን እንዲፈናቀሉ እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

በአሁኑ ወቅት በኮሪደር ልማትና በጫካ ፕሮጀክት ፕሮጀክቶች አማካኝነት በመቶ ሺ የሚቆጠሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተፈናቅለው ወደተለያዩ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ የተደረገ ሲሆን በዚህኛው ፕሮጀክትም በርካታ ነዋሪዎች ተመሳሳይ እጣ እንደሚገጥማቸውም አስታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...