ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ 1,100 ሕጻናት መቁሰላቸውን ወይም መሞታቸውን ተገለፀ

Date:


በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ጦርነት “በቀጣናው ለሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናት እሰቃቂ ነው” ሲል የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት ኤጀንሲ (ዩኒሴፍ) አስታወቀ።


አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21/2018 ዓ.ም. ኢራን ላይ ጥቃት ከከፈቱበት ዕለት አንስቶ ከ1,100 በላይ ሕጻናት ጉዳት ወይም ሞት እንደደረሰባቸው ዩኒሴፍ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።


መግለጫው አክሎም ይህ መረጃ በኢራን የተገደሉ 200፣ በሊባኖስ 91፣ በእስራኤል አራት እንዲሁም በኩዌት አንድ ሕፃናትን ያጠቃልላል።
ዩኒሴፍ “የሕፃናትን መገደል እና የአካልጉዳት ማድረስ ወይም ሕጻናት የሚገለገሉባቸውን አስፈላጊ አገልግሎቶች ማውደም እና መቋረጥ ምንም ምከንያት የሚቀርብበት ነገር አይደለም “ ብሏል።


ድርጅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ተዋጊ አካላት “ጦርነቱን ቆሞ ወደ ዲፕሎማሲ ድርድር እንዲመጡ” ያቀረቡትን ጥሪ በድጋሚ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።


በተጨማሪም በጦርነት የሚሳተፉ አካላት “በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ፣ ይህም ሕፃናትን የሚጎዱ ፈንጂዎችን ከመጠቀም መቆጠብን ጨምሮ፣ የጦር መሳሪያዎችን በመምረጥ ረገድ ሁሉንም አስፈላጊ ጥንቃቄዎች እንዲወስዱ” ጥሪ አቅርቧል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...