የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጥቃት በጽኑ በመቃወም፣ መንግሥታቸው ማንኛውንም ዓይነት የጦርነት አማራጭ እንደማይደግፍ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የስፔን ሕዝብ ይህንን ቀውስ እንደሚቃወም ገልጸው፣ እ.ኤ.አ. በ2003 የተካሄደው የኢራቅ ወረራ ዓለምን ይበልጥ ደህንነቱ ያልተጠበቀ ማድረጉን እንደ ትልቅ ትምህርት አንስተዋል።
አሁንም በኢራን ላይ የሚደረገው ጥቃት ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ ሥርዓትን እንደማያመጣና ለሰው ልጅ ሕይወት መሻሻል ፋይዳ እንደሌለው አስገንዝበዋል።
ሳንቼዝ አሁን ያለውን ውጥረት “የሰው ልጅ ታላላቅ አደጋዎች መጀመሪያ” ሲሉ በመግለጽ፣ መንግሥታት በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ዕጣ ፈንታ ላይ ቁማር መጫወት የለባቸውም ሲሉ አሳስበዋል።
