“ጦርነት መፍትሔ አይደለም”

Date:

የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጥቃት በጽኑ በመቃወም፣ መንግሥታቸው ማንኛውንም ዓይነት የጦርነት አማራጭ እንደማይደግፍ አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የስፔን ሕዝብ ይህንን ቀውስ እንደሚቃወም ገልጸው፣ እ.ኤ.አ. በ2003 የተካሄደው የኢራቅ ወረራ ዓለምን ይበልጥ ደህንነቱ ያልተጠበቀ ማድረጉን እንደ ትልቅ ትምህርት አንስተዋል።

አሁንም በኢራን ላይ የሚደረገው ጥቃት ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ ሥርዓትን እንደማያመጣና ለሰው ልጅ ሕይወት መሻሻል ፋይዳ እንደሌለው አስገንዝበዋል።

ሳንቼዝ አሁን ያለውን ውጥረት “የሰው ልጅ ታላላቅ አደጋዎች መጀመሪያ” ሲሉ በመግለጽ፣ መንግሥታት በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ዕጣ ፈንታ ላይ ቁማር መጫወት የለባቸውም ሲሉ አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...