«ፍትህ በግፍ እየሞቱ ላሉ እና ትኩረት ለተነፈጋቸው ንፁሀን ወገኖቻችን»

Date:

የአክብሮት ሰላምታዬን በማስቀደም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለታሪካዊውና አንጸባራቂው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ የሚል መልዕክቴን ሳስተላልፍ በታላቅ ብሄራዊ ኩራት ነው፡፡

የዘንድሮውን ፻፴ ኛው የአድዋ ድል በዓል ስናከብር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራችን ባለው የፖለቲካ አለመረጋጋት ሳቢያ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እስካሁኗ ሰዓት ድረስ በማንነታቸው ብቻ ተለይተው እጅግ ኢ-ሰብዓዊ በሆነ መንገድ በአሰቃቂ ሁኔታ በግፍ እየተገደሉ ያሉ

እንዲሁም የአካል እና የስነልቦና ጕዳት የሚደርስባቸው ብሎም ከቤት ንብረታቸው ከቀያቸው የሚፈናቀሉ ንፁሀን ወገኖቻችንን በህሊና ፀሎት እያሰብን እና ለዚህም እየተባባሰ ለመጣው ትኩረትም ለተነፈገው ማህበራዊና ሀገራዊ ቀውስ መንስኤው ሀገራችን ኢትዮጵያን ላለፏት ቀላል ለማይባሉ አመታት ቁልቁል ሰብቆ የያዛት የዘር ፖለቲካ መሆኑን አፅንኦት በመስጠት

ከመቼውም ጊዜ በላቀ መላው ኢትዮጵያውያን ዘር ሀይማኖት ሳንለይ በአንድነት በመቆም ለጋራ ህልውናችን ስጋት የሆነውን ጎሳን መሰረት ያደረገ ስርዓት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በቃ ልንለው የሚገባ መሆኑን በጥብቅ በማሳሰብም ጭምር ነው።

«ፍትህ በግፍ እየሞቱ ላሉ እና ትኩረት ለተነፈፖ ንፁሀን ወገኖቻችን»

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፍል!

ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...