በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ፒኤስጂ ከአርሰናል ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 ማሸነፍ ችሏል።
የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግብ ኦስማን ዴምበሌ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
በጨዋታው የፒኤስጂው የፊት መስመር ተጨዋች ኦስማን ዴምበሌ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል።
በሌላ በኩል የአርሰናሉ የመስመር ተጨዋች ጁሪየን ቲምበር ጉዳት አጋጥሞታል።
የመልስ ጨዋታው በሚቀጥለው ሳምንት ፓሪስ ላይ የሚደረግ ይሆናል።
