ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሁለት ወይም ሦስት ሳምንት ውስጥ ኢራንን በኃይለኛው እንደሚመቱ ተናገሩ

Date:

የአሜሪካ ፕሬዝዳት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥለው ከሁለት እስከ ሦስት ሳምንት ባለ ጊዜ ውስጥ ኢራን ላይ “እጅግ ኃይለኛ” የሆነ ጥቃት በመፈጸም የጀመሩትን ተግባር “በጣም በፍጥነት” እንደሚያጠናቅቁ አስታወቁ።

ትራምፕ ትናንት ምሽት ለአገሪቱ ሕዝብ ባደረጉት በቴሌቪዥን የተላለፈ ንግግር የአሜሪካ ጦር በኢራን ጦርነት ሊያሳካ የፈለጋቸው ግቦች ላይ ለመድረስ መቃረቡን ገልጸዋል። ጦርነቱ መቼ ይጠናቀቃል ለሚለው ግን የጊዜ ሰሌዳ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ትራምፕ ባደረጉት ንግግር፤ በኢራን በተዘጋው የሆርሙዝ ውሽመጥ በኩል የሚያልፍ ነዳጅ የሚረከቡ አገራት “ድፍረት” በማሳየት ወሳኙን መተላለፊያ እንዲቆጣጠሩ ጠይቀዋል።

ትራምፕ 20 ደቂቃ ገደማ የፈጀው የዋይት ሀውስ ንግግራቸው፤ አሜሪካ በዚህ ጦርነት የያዘቻቸው “ዋነኛ ስትራቴጂክ ግቦች ሊጠናቀቁ እንደተቃረቡ” ተናግረዋል። የኢራን ባሕር ኃይል የድሮን እና ባለስቲክ ሚሳኤል ጦሮች “ተደምስሰዋል” ብለዋል።

“በጣም በአጭር ጊዜ ውስጥ፤ በሚቀጥለው ከሁለት እስከ ሦስት ሳምንት በሚሆን ጊዜ ውስጥ እጅግ በኃይለኛው እንመታቸዋለን” ሲሉ ዝተዋል።

ፕሬዝዳንቱ ከኢራን አመራር ጋር “እየተካሄደ ነው” ስላሉት ንግግር ዝርዝር መረጃዎች ከመስጠት ተቆጥበዋል። ድርድርሩ ፍሬ አልባ የሚሆን ከሆነ የኢራንን የኢነርጂ መሠረተ ልማት እንደሚመቱም ጠቁመዋል።

“ስምምነት ላይ ካልተደረሰ እያንዳንዱን የኤሌትሪክ ኃይል ማመንጫ በጣም በኃይለኛው እንመታለን፤ ምናልባትም ተመሳሳይ ጊዜ ላይ” ብለዋል።

“ምንም እንኳ ከሁሉም አንጻር ቀላሉ ዒላማ ቢሆንም ነዳጃቸውን አልመታንም፤ ምክንያቱም የመትረፍ ወይም መልሶ የመገንባት ትንሽም እንኳ ዕድል አይሰጣቸውም” ሲሉ ተደምጠዋል።

ትራምፕ ከዚህ ንግግራቸው አስቀድሞ የኢራን የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠይቃለች በማለት ጽፈው ነበር። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቶሎ በሰጠው ምላሽ የፕሬዝዳንቱን ገለጻ “ሐሰት እና መሠረተ ቢስ” ብሎታል።

ትናንቱ ንግግራቸው ከዚህ ቀደም እንዳደረጉት ሁሉ የአሜሪካ አጋሮች የሆርሙዝ ወሽመጥን ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲንቀሳቀሱ ጠይቀዋል። “ቢዘገይም ድፍረት አሳዩ” እንዲሁም “እንዲሁ ወደ ወሽመጡ ሄዳችሁ ያዙት” ብለዋል።

አገራቸውን ከኔቶ የማስወጣት ሐሳብ እንዳላቸው ሲገልጹ የነበሩት ትራምፕ፤ በዚህ ንግግራቸው ከወታደራዊው ጥምረት ጋር ወደፊት ስለሚኖረው ሁኔታ አልጠቀሱም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...

አደይ ኢትዮጵያ ጓል አስመራ…!!

የቀድሞ ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የስንብት ቃል ለጠቅላይ ሚ/ር ዐብይ...

ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ሁለተኛው ዙር ድርድር ሊደረግ እንደሚችል ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ሁለተኛ ዙር የሰላም ድርድር...

በ”ፊንቴክ” ኢንቨስትመንት በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ጊዜ ተፈቀደለት

ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው...