100 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን ስምሪት ገብተዋል

Date:

ዛሬ በከተማችን ያለውን የቡዝሃን ትራንስፖርት እጥረት እና የነዋሪዎችን እንግልት የሚቀንሱ 100 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን በመግዛት ወደ ስምሪት አስገብተናል።

የITS (ኢንተለጀንት የትራንስፖርት ሥርዓት) እና FCS (የታሪፍ ስብስብ ሥርዓት) ቴክኖሎጂን በተቀናጀ መልኩ በስራ ላይ ያዋሉት እነዚህ አውቶቢሶች ከአየር ብክለት ነፃ፣ ምቹ፣ በአንድ ጊዜ በርካታ የሠው ቁጥር ማጓጓዝ የሚችሉ፣ ዘመናዊና ተደራሽ፣ ወጪ ቆጣቢ፣ አስተማማኝ፣ ለአውቶቡስ ብቻ በተፈቀደ መስመር ስለሚጓዙ ፈጣን አገልግሎት የሚሰጡ እንዲሁም ለነዳጅ ይወጣ የነበረውን ወጪ የሚቀንሱ ናቸው።

ወደ አገልግሎት የገቡት እነዚህ 100 የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች በዛሬው እለት በሁሉም የከተማችን አቅጣጫዎች ለነዋሪዎቻችን ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል።

የህዝባችንን እንግልት ለመቀነስ የጀመርነውን ራዕይ በመጋራት በመንግስትና የግል አጋርነት መርሃግብር የመጀመሪያው የትራንስፖርት ኦፕሬተር በመሆን ዛሬ አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ በነዋሪዎቻችን ስም ላመሰግነው እወዳለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...