2 ነጥብ 6 ሚሊየን ዓመታትን ያስቆጠረ የሰው ልጅ ዝርያ በአፋር ክልል ተገኘ

Date:

2 ነጥብ 6 ሚሊየን ዓመታትን ያስቆጠረ እና ፓራንትሮፕስ የሚል ስያሜ ያለው የሰው ልጅ ዝርያ በአፋር ክልል ሚሌ ሎጊያ በተባለ ስፍራ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር በሰጡት መግለጫ፥ ባለስልጣኑ ከሚያከናውናቸው ሥራዎች አንዱ የሰው ልጅ ቅሪት አካላት ላይ ምርምር ማድረግ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ተመራማሪዎች ከውጭ ሀገራ ተመራማሪዎች ጋር በመሆን ባደረጉት ጥናትና ምርምር አትዮጵያ የሰው ዘር መገኛነቷን በዓለም መድረክ አስተዋውቀዋል ነው ያሉት።

በዛሬው ዕለትም ከዚህ በፊት ያልታዬ የሰው ልጅ ዝርያ በአሜሪካ የችካጎ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ በሆኑት ዘረሰናይ ዓለምሰገድ (ፕ/ር) በተመራ ልዑክ መገኘቱን ተናግረዋል።

ግኝቱ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን እና ለአንተሮፖሎጂ ምርምር ኢትዮጵያ እና የአፋር ክልል ተመራጭ መሆናቸውን የበለጠ የሚያረጋግጥ መሆኑን አመላክተዋል።

ግኝቱ በዓለም ላይ ታዋቂ በሆነው ኔቸር መጽሔት ላይ በዛሬው ዕለት እንደሚታተም ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...