2 ነጥብ 6 ሚሊየን ዓመታትን ያስቆጠረ የሰው ልጅ ዝርያ በአፋር ክልል ተገኘ

Date:

2 ነጥብ 6 ሚሊየን ዓመታትን ያስቆጠረ እና ፓራንትሮፕስ የሚል ስያሜ ያለው የሰው ልጅ ዝርያ በአፋር ክልል ሚሌ ሎጊያ በተባለ ስፍራ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር በሰጡት መግለጫ፥ ባለስልጣኑ ከሚያከናውናቸው ሥራዎች አንዱ የሰው ልጅ ቅሪት አካላት ላይ ምርምር ማድረግ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ተመራማሪዎች ከውጭ ሀገራ ተመራማሪዎች ጋር በመሆን ባደረጉት ጥናትና ምርምር አትዮጵያ የሰው ዘር መገኛነቷን በዓለም መድረክ አስተዋውቀዋል ነው ያሉት።

በዛሬው ዕለትም ከዚህ በፊት ያልታዬ የሰው ልጅ ዝርያ በአሜሪካ የችካጎ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ በሆኑት ዘረሰናይ ዓለምሰገድ (ፕ/ር) በተመራ ልዑክ መገኘቱን ተናግረዋል።

ግኝቱ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን እና ለአንተሮፖሎጂ ምርምር ኢትዮጵያ እና የአፋር ክልል ተመራጭ መሆናቸውን የበለጠ የሚያረጋግጥ መሆኑን አመላክተዋል።

ግኝቱ በዓለም ላይ ታዋቂ በሆነው ኔቸር መጽሔት ላይ በዛሬው ዕለት እንደሚታተም ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...