232 መንገደኞችን አሳፍሮ የነበረ አውሮፕላን በህንድ ተከሰከሰ

Date:

232 መንገደኞችን አሳፍሮ ወደለንደን ያመራ የነበረ የኤር ኢንዲያ ንብረት የሆነው ቦይንግ 787 ድሪም ላይነር አውሮፕላን ከተነሳ በኋላ መከስከሱ ተሰማ።

አውሮፕላኑ ከአህመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ በተነሳበት ቅፅበት መከስከሱን ቢቢሲ አስነብቧል።

በወቅቱ 12 የአውሮፕላኑን ሰራተኞች ጨምሮ 232 መንገደኞችን አሳፍሮ የነበረ ሲሆን፥ ከተነሳ በኋላ በ190 ሜትር ከፍታ ላይ ከአየር በረራ ተቆጣጣሪዎች ጋር የመጨረሻ ግንኙነት አድርጓል ተብሏል።

የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልተገለጸ ሲሆን፥ አውሮፕላኑ በመኖሪያ መንደር አካባቢ መከስከሱንም ነው ዘገባው ያመላከተው።

በህይወት ሰው ስለመትረፉ ምንም የተባለ ነገር የለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...