24 የተሽከርካሪ ዓመታዊ ቴክኒክ ምርመራ ተቋማት ላይ ርምጃ ተወሰደ

Date:

24 የተሽከርካሪ ዓመታዊ ቴክኒክ ምርመራ ተቋማት ላይ ርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ የተሽከርካሪ ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ ተቋማትን በመገምገም ነው የጎላ ክፍተት የተገኘባቸው 24 ተቋማት ላይ ርምጃ የወሰደው፡፡

በዚህ መሰረትም 2 የምርመራ ተቋማት ፈቃዳቸው የተሰረዘ ሲሆን÷ 4 ተቋማት ደግሞ ለሶስት ወራት ታግደው ክፍተታቸውን እንዲያርሙ ተወስኗል፡፡

በተጨማሪም 6 ተቋማት ለአንድ ወር ሥራ እንዲያቆሙ እንዲሁም 12 ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በቀጣይ የመዲናዋ ነዋሪዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ በቁርጠኝት እንደሚሰራም ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...