ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ተሾመለት

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ሆነው ለተሾሙት አቶ ባረክ ታደሰ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሸዊት ሻንካ የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የኢትዮጵያውያን ቤት እንድሆን እንሰራለን፤ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የተሻለ ውጤት እንድመዘገብ የአሰራር መመሪያዎችንና ደንቦችን ተከትሎ የሚተገብርና የሚያስተገብር አመራር መኖር ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ዘርፉን ወደ ተፈለገው ደረጃ ከፍ ለማድረግም ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ባረክ ታደሰ ትልቅ አቅም በመሆናቸው እንኳን ደህና መጡ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት አቶ ባረክ ታደሰ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ልባዊ ምስጋና በማቅረብ ሀገራችን በኪነጥበቡ ዘርፍ ተጠቃሚ እንድትሆን ሁሉን ያማከለ ኪናዊ ስራዎችን ከታችኛው አደረጃጀት ጀምሮ በጋራ መስራትን ይጠይቃል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ የተሰጠኝን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣትም አቅጣጫ ሰጭ ከፍተኛ አመራሮች ከጉኔ በመኖራቸው እድለኛ ነኝ ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...