27ኛው አዲስ ቻምበር ዓለም አቀፍ ንግድ ትርኢት በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

Date:

የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት “ዘላቂ ንግድ፤ የንግድ ተወዳዳሪነት በኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው 27ኛው አዲስ ቻምበር ዓለም አቀፍ ንግድ ትርኢት ከሚያዝያ 15 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ይካሄዳል።

ለሦስት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ ላይ ከተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተወጣጡ 150 የአገር ውስጥና የውጭ ሀገር ተሳታፊዎች ምርትና አገልግሎታቸውን እንደሚያስተዋውቁ ምክር ቤቱ ገልጿል።

የንግድ ትርኢቱ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ7፡00 ሰዓት ጀምሮ በኤግዚቢሽን ማዕከል ይከናወናል ተብሏል።

በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ይጠበቃልል።

ይህ ንግድ ትርኢት ተሳታፊዎች የንግድ ለንግድ ግንኙነት እንዲፈጥሩ፣ ልምድ እንዲቀዋወጡና ለድንበር ተሻጋሪ ሽርክና ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተገልጾአል።

ምክር ቤቱ መሰል ዓለም አቀፍ የንግድ ትርኢቶችን ማዘጋጀቱ በሀገሪቱ የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዲስፋፋ በማድረግ ለኢኮኖሚ መነቃቃት የላቀ ፋይዳ እንዳለው አስታውቋል።

ተቋሙ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማገዝ የሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት አካል የሆነው ይህ ዝግጅት፣ ለፈጠራና ለዘላቂ የንግድ ተወዳዳሪነት ልዩ መድረክ እንደሚሆንም ተገልጿል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...

በ’ፊንቴክ’ የማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠ

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ስም በተፈጸመ  የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር...

የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያደረጉት የኢንቨስመንት መጠን 723 ሚሊዮን ዩሮ መድረሱ ተሰማ

ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች  በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን...

የቴሌግራም ማስጠንቀቂያ

ቴሌግራም (Telegram) ኦፊሴላዊ ያልሆኑ የቴሌግራም መተግበሪያዎችን (Unofficial Apps) በሚጠቀሙ...