የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል ለማስተዋወቅ ያለመው 3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ከግንቦት 4 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።

ይህ ፎረም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን (ኢኢኮ)፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በልማት አጋር ድርጅቶች ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ፎረሙ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ትኩረት እና አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ አመልክተዋል።
ባለፈው ዓመት በተካሄደው 2ኛው የኢንቨስት ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ከ750 በላይ ድርጅቶች መሳተፋቸውንና ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት ለማድረግ ቃል የተገባበት እንደነበር አስታውቀዋል።
