3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

Date:

የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዕድል ለማስተዋወቅ ያለመው 3ኛው ኢንቨስት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም ከግንቦት 4 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።

ይህ ፎረም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን (ኢኢኮ)፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በልማት አጋር ድርጅቶች ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ፎረሙ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ትኩረት እና አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ አመልክተዋል።

ባለፈው ዓመት በተካሄደው 2ኛው የኢንቨስት ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም ከ750 በላይ ድርጅቶች መሳተፋቸውንና ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት ለማድረግ ቃል የተገባበት እንደነበር አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...