5 የገበታ ጨዉ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ተነገረ

Date:

የጥንቃቄ #መልክት

የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች በሚመለከተው አካል የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳይሰጣቸውና ጥራትና ደረጃቸው ሳይረጋገጥ ገበያ ላይ በመገኘታቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለስልጣኑ አሳሰበ፡፡

አዲስ አበባ፡ መጋቢት 4፣2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በቅርቡ ገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር አምስት የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳያገኙ ምልክቱን ለጥፈው ገበያ ላይ ውለው ተገኝተዋል፤በመሆኑም እነዚህ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለሰልጣኑ ያሳስባል፡፡

ምስላቸው እና ዝርዝራቸው ከዚህ በታች የተቀመጡ የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ ደረጃ ምልክቱን የመጠቀም ፈቃድ ያላገኙና ጥራት እና ደህንነታቸው ያልተረጋገጠ በመሆናቸው ያሳውቃል፡፡

  1. ሊኑ የገበታ ጨው /LINU IODIZED SALT /፣
  2. ታሪክ የገበታ ጨው /TARIK TABLE SALT /፣
  3. SALT BAY፣
  4. ሺማ አዮዳይዝድ ጨው /SHIMA IODIZED SALT/
  5. እና ጂ.ኤም ኤዳይዝድ ጨው /G.M Iodized salt/ በሚባል የምርት ስም የሚጠሩ ናቸው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...