5 የገበታ ጨዉ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ተነገረ

Date:

የጥንቃቄ #መልክት

የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች በሚመለከተው አካል የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳይሰጣቸውና ጥራትና ደረጃቸው ሳይረጋገጥ ገበያ ላይ በመገኘታቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለስልጣኑ አሳሰበ፡፡

አዲስ አበባ፡ መጋቢት 4፣2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በቅርቡ ገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር አምስት የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳያገኙ ምልክቱን ለጥፈው ገበያ ላይ ውለው ተገኝተዋል፤በመሆኑም እነዚህ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለሰልጣኑ ያሳስባል፡፡

ምስላቸው እና ዝርዝራቸው ከዚህ በታች የተቀመጡ የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ ደረጃ ምልክቱን የመጠቀም ፈቃድ ያላገኙና ጥራት እና ደህንነታቸው ያልተረጋገጠ በመሆናቸው ያሳውቃል፡፡

  1. ሊኑ የገበታ ጨው /LINU IODIZED SALT /፣
  2. ታሪክ የገበታ ጨው /TARIK TABLE SALT /፣
  3. SALT BAY፣
  4. ሺማ አዮዳይዝድ ጨው /SHIMA IODIZED SALT/
  5. እና ጂ.ኤም ኤዳይዝድ ጨው /G.M Iodized salt/ በሚባል የምርት ስም የሚጠሩ ናቸው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...