905 የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ሀገር አቀፍ የደንበኞች ጥሪን  ሊያስተናግድ ነው

Date:

የኢትዮጵያ  ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ብቻ ተወስኖ የቆየውን 905 አጭር  ሥልክ ቁጥር የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ወደ ሀገር አቀፍ ደረጃ ሊያሳድግ ነው።

አዲስ አበባ ላይ ብቻ ተወሰኖ  የነበረው  የደንበኞች የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ከ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ጀምሮ ሀገር አቀፍ ሊደረግ ነው።

የአገልግሎቱ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ኃላፊ ስምረት በለጠ  እንደተናገሩት፤ የደንበኞችን ጥሪ የመቀበል አቅም በማሳደግ የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ሀገር አቀፍ ለማድረግ  የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል።

ቀደም ሲል የጥሪ ማዕከሉ 905 በመባል ለአዲስ አበባ ከተማ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች ብቻ  የጥሪ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር ጠቅሰው፤ ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ባደረገው ሪፎርም የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል በአዲስ መልኩ እንዲደራጅ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡

Gazette_Plus

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...