በአሜሪካዋ የቴክሳስ ግዛት በደረሰ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ቢያንስ 78 ሰዎች ሲሞቱ፣ ከሟቾቹ መካከል 28ቱ ሕጻናት ናቸው ተብሏል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስፍራውን እንደሚጎበኙ የተጠቆመ ሲሆን ክስተቱን “አስደንጋጭ እና አሰቃቂ” ሲሉ ገልፀውታል።
የቴክሳስ ባለሥልጣናት የጠፉትን ሰዎች ቁጥር ማረጋገጥ ባይችሉም ፍለጋው እና የነፍስ አድን ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
ባለፈው አርብ “የጓንዳሉፔ” ወንዝ ባስከተለውከባድ ጎርፍ በሕይወት እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የዘገበው ሮይተርስ ነው።
