ሁለት ቤተመንግስቶች የባለ አምስት ኮከብ ሆቴል አገልግሎት መስጠት ሊጀምሩ ነው

Date:

በኢትዮጵያ ቤተመንግስት አስተዳደር ስር የሚተዳደሩት ድሬዳዋ ቤተ መንግስት እና የጅማ ግቤ አዳራሽ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል የሚያደርጋቸው ግንባታ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መድረሱን አራዳ ከኢትዮጵያ ቤተ መንግስት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ምትኩ ኩምሳ ሰምቷል።

የድሬዳዋ ቤተመንግስት የሆቴል ግንባታው ከሦስት ዓመታት በፊት ተጀምሮ አሁን ወደ መጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ደርሷል ተብሏል።

በጅማ የሚገኘው ግቤ አራዳሽ የሆቴሉ ግንባታ በሸራተን አዲስ ሆቴል ድርጅት የተከናወነ ሲሆን፣፥ ሸራተን ኢንቨስት ያደረገበትን ሆቴል ለሦስት ዓመታት ወጪውን ለመተካት ከተገለገለበት በኋላ ለቦታው የኪራይ ክፍያ ለመንግስት መፈፀም እንደሚጀምር ተመላክቷል።

በሁለቱም ቤተመንግስቶች ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ የኢትዮጵያ ንጉስ ሳሉ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ቤቶች የቅርስ ይዘታቸው ሳይነካ ተጨማሪ ግንባታዎችን በማከል ለአገልግሎት ዝግጁ እየተደረጉ መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...