ሰርጌይ ላቭሮቭ ከሰሜን ኮሪያው ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

Date:

የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ወደ ሰሜን ኮሪያ በማቅናት ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ጋር ተወያዩ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሰሜን ኮሪያው ፕሬዚዳንት ጋር መገናኘታቸውን በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ያጋሩ ሲሆን፤ እስከ እሑድ ድረስ እዚያው ቆይተው በተለያዩ ጉዳዮች ከሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመርክሩ ተዘግቧል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝት የሁለቱ ሀገራትን ወታደራዊ ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል ማሳያ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ኪም ከኒውክሌር የጦር መሣሪያ ጋር ተያይዞ ከውጭ ለሚደረግባቸው ጫና የሩሲያን ቴክኖሎጂ ሽግግር እንደሚፈልጉ ተጠቅሷል።

ላቭሮቭ ፕሬዚዳንቱን ከማግኘታቸው በፊት፤ በምሥራቅ የሀገሪቱ ባሕር ዳርቻ በምትገኘው ቮንሳን ከተማ በቅርቡ በተከፈተው ትልቅ ሪዞርት ውስጥ ከአቻቸው ከቾ ሶን ሁ ጋር ተወያይተዋል።

ሰሜን ኮሪያ በዩክሬን ጦርነት ላይ ወታደሮቿን በመላክ ላደረገችላቸው ድጋፍ ያመሰገኑት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ ከፕሬዚዳንቱ ጋር ስለጦርነቱ ሁኔታ እና ቀጣይ ድጋፍ መወያታቸውን ታስ የዜና ወኪልን ጠቅሶ የዘገበው እልጄዚራ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...