በጋምቤላ ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከሰተ

Date:

በጋምቤላ ከተማ ሌሊቱን በጣለው ከባድ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል ። በተለይ በ05 ቀበሌ አንዳንድ አካባቢ የግለሰቦች መኖሪያ ቤት ውስጥ በመግባት በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን የእግረኛ እና የመኪና መንገዶች ላይም ውሃ ስለተኛባቸው ለመተላለፍ አስቸጋሪ አድርጎታል ።

የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ሳይመን ሙን ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ከክረምት ዝናብ ጋር ተያይዞ በሰውና ንብረት ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል ።

የጎርፍ መፋሰሻ ቱቦዎችን በመክፈት የውሃ ፍሰትን መቆጣጠር እንደሚገባ ገልጸዋል ።

የክረምት ወራት ገና ከመሆኑ የተነሳ የዝናብ መጠን ሊጨምር ስለሚችል የከተማችን ነዋሪዎች ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባቸው ጨምረው ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...