የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወረቀት ነጻ ለማድረግ የሚያግዝ ‘ሲስተም’ ወደ ሥራ ገባ

Date:

ሰከላ የተሰኘና በትምህርት ሚኒስቴር ስርአተ ትምህርት መሰረት እስከ12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም መጽሐፍትና አጋዥ ማጣቀሻዎችን በተንቀሳቃሽ ምስል እና በድምጽ የሚያካትት የቴክኖሎጂ ስርዓት ወደ ስራ ገብቷል።

ቴክኖሎጂው የትምህርት አስተዳደርና አካዳሚክ ስራዎችን፣ የወላጆችና የትምህርት ቤት እንዲሁም የተማሪና አስተማሪ ግንኙነትን ለማሳለጥ እንደሚረዳ ተገልጿል።

‘ሲስተሙ’ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የበለጸገና በተለያዩ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መጠቀም የሚያስችል ነው።

ማንኛውም የትምህርት ተቋምም በsekela.appዌብሳይት ላይ በመመዝገብና መረጃን በማስገባት በጥቂት ቀናት ውስጥ ተቋሙን ማዘመን እንደሚችል ተመላክቷል።

የሰከላ ‘ሲስተም’ ከገጠር እስከ ከተማ ያሉትን ትምህርት ቤቶች በኔትዎርክ በማገናኘት ሀገራዊ መረጃን በመሰብሰብ ተዓማኒነት ያለው ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል ጭምር እንደሆነ ሰምተናል።

የቴሌኮም አገልግሎትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎችና በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርት ለተቋረጠባቸው ቦታዎች የሚያደርጉትን ጥረት ይህ ‘ሲስተም’ የሚያግዝ በመሆኑም በጋራ መግባባት መስራት እንደሚቻል ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...