ፕሬዝደንት ሩቶ ሆስፒታሎች ለውጭ ታካሚዎች የሚያስከፍሉትን ክፍያ “ህገወጥ” ሲሉ አወገዙ
ፕሬዝደንት ዊልያም ሩቶ ሆስፒታሎች ለአዳዲስ የጤና አጠባበቅ ፕሮግራሞች ውል ተብሎ ለሚታከሙ (outpatient) ታካሚዎች ክፍያ እንዳይጠይቁ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።
የኬኒያው ፕሬዝደንቱ ይህን የተናገሩት በሀገሪቱ በአዲስ የጤና አጠባበቅ ፕሮግራም ስር እንዲህ አይነት ክፍያ መጠየቅ ህገወጥ ነው በሚል ነው።
ፕሬዝደንቱ ዜጎች እንደዚህ አይነት ህገወጥ ጥያቄዎችን እንዲቃወሙ እና ክፍያ የሚጠይቁ ሆስፒታሎችን ለፖሊስ እንዲያሳውቁ አሳስበዋል።
ይህ መመሪያ አዲሱ የጤና አጠባበቅ ስርዓት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እየሆነ ባለበት በዚህ ወቅት የመጣ ሲሆን የጤና አገልግሎቶች ለሁሉም ኬንያውያን በነፃ ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።
