በግምጃ ቤት ጨረታ ገንዘብ ሚኒስቴር ከእቅዱ በላይ ገዛ

Date:

ከትላንት በስቲያ ረቡእ ነሃሴ 14 በተደረገው የግምጃ ቤት ጨረታ ከፍተኛ ገንዘብ ቢቀርብም ብሄራዊ ባንክ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ለመግዛት ሳይፈቅድ ቀረ፡፡

ይህ ሁኔታ ሲደገም በ15 ቀናት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡

ረቡዕ በነበረው ጨረታ መንግስት ለመግዛት አስቦ የነበረው 19.7 ቢሊየን ብር መሆኑን አስታውቆ የነበረ ቢሆንም በጠቅላላው 41.9 ቢሊየን ብር (ከእቅዱ የ113 በመቶ ጭማሪ ያለው) ገንዘብ ለግምጃ ቤት ግዥ ቀርቦ ነበር፡፡

በጨረታው መንግስት 19.6 ቢሊየን ብር የሚሆነውን የገዛ ሲሆን ይህም የበጀት አመቱ ሲጀመር እስከ መስከረም በሚደረጉ ጨረታዎች እገዛዋለው ብሎ ካስቀመጠው እቅድ ከፍ ያለ ነው፡፡

መንግስት ለነሃሴ 14 ለመግዛት አቅዶ የነበረው 14.7 ቢሊየን ብር ነበር ሆኖም እሮብ በተደረገው ጨረታ የገዛው ወደ 20 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ነው፡፡

ከወለድ አንፃር መቶኛው መቀነስ አሳይቷል፡፡ በጉዳዩ ላይ በቅዳሜ ገበያ የሬድዮ ጥንቅር ከጥቂት ሳምንታት በፊት እንደጠቀስነው መንግስት ለግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ የሚሰጠው ወለድ እየቀነሰ እንዲሄድ ፍላጎት እንዳለው ከፍተኛ የመንግስት ባላስልጣን ምንጮቻችንን ጠቅሰን መግለጻችን አይዘነጋም::

KGEthiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...