ከጢስ ዓባይ ቀጥሎ በኢትዮጵያ 2ኛው ትልቁ ፏፏቴ

Date:


የሶር ፏፏቴ በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦር ዞን በቾ ወረዳ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ ፏፏቴው ከኢሉ አባቦር ዞን መቱ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ የቱርስት መስህብ ቢሆንም መሰረተ ልማቶች ባለመሟላታቸው በጎብኝዎች ዘንድ ብዙም ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡

ሶር የተሰኘው ወንዝ የፏፏቴው መነሻ ሲሆን፤ ወንዙ የመቱን ከተማ አቋርጦ የሚያያልፍ ነው፡፡

በስፋቱም ሆነ በርዝመቱ ከጢስ ዓባይ ቀጥሎ ትልቅ እንደሆነ የሚነገርለት ሶር ፏፏቴ፤ ወቅቶች ሲፈራረቁ የፏፏቴው መጠን ከፍ እና ዝቅ እንደሚል ይነገራል፡፡

ይህ የተፈጥሮ መስህብ ትኩረት ተሰጥቶት መልማት ቢችል በቱሪዝም ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የድርሻውን ገቢ ማበርከት የሚችል የተፈጥሮ ሀብት መሆኑ ይገለፃል፡፡

ዙሪያውን በተፈጥሮ ቡና እና ጥቅጥቅ ባለ ደን የተከበበው ሶር ፏፏቴ፣ የቱሪስቶችን ቀልብ ለመግዛት የሚያስችል አስደናቂ መልክዓ ምድርንም የተላበሰ ነው፡፡

50 ሜትር ቁመት እና 78 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ፏፏቴው፤ ወደ ታች በሚንደረደርበት ወቅት ልክ እንደ ጢስ ዓባይ ለአካባቢው ልዩ ውበት እንደሚያላብሰው ይነገራል፡፡

የሶር ፏፏቴ ከአስደናቂ መልክዓ ምድሩ በተጨማሪ፤ እንደ ዝንጀሮ፣ ጉሬዛ እና ድኩላ ያሉ የዱር እንስሳትን አስጠልሎ ይገኛል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...

ሕወሓት ድብረጺዮንን የክልሉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

የክልሉ ፕሬዚዳንት ተደርገው የተመረጡት  ድብርጺዮን ገ/ ሚካዔል (ዶ/ር)  ቃለ...