ዘመን ገበያ አዲስ አመት ኤግዚቢሽን እና ባዛር በታሜሶል ኮሚዩኒኬሽን አዘጋጅነት ሊካሄድ ነው

Date:

የ2017 ዓ.ም የዘመን ገበያ አዲስ አመት ኤግዚቢሽንና ባዛርን ለማዘጋጀት ታሜሶል ኮሚዩኒኬሽን በ92.8 ሚሊዮን ብር ጨረታ ማሸነፉ ተገልጿል ።

ይህ ትልቅ ዝግጅት “ዘመን ገበያ አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት ኤክስፖ 2018” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከነሐሴ 17 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።

ዝግጅቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በሽርክና የሚዘጋጅ ሲሆን፣ የቴሌብር ሱፐርአፕን ለህብረተሰቡ በስፋት ለማስተዋወቅ ታስቦበት እንደሆነም ታውቋል።

በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ300 በላይ የአገር ውስጥ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጪዎች የሚሳተፉ ሲሆን፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከቻይና፣ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ከሌሎች ሀገራት የመጡ ኤግዚቢተሮችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።

የኤግዚቢሽኑ ተሳታፊዎች ለህብረተሰቡ ሰፊ ምርጫ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ከትምህርት ቁሳቁስ፣ የቤት እቃዎች እና ቴክኖሎጂን ጨምሮ የተለያዩ የፍጆታ ዕቃዎች ይቀርባሉ ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ፣ ዋና ዋና ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙበት ልዩ “ፋይናንስ መንደር” የሚል ቦታ መዘጋጀቱ በዝግጅቱ ላይ ተጨማሪ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...

ሕወሓት ድብረጺዮንን የክልሉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

የክልሉ ፕሬዚዳንት ተደርገው የተመረጡት  ድብርጺዮን ገ/ ሚካዔል (ዶ/ር)  ቃለ...