ኦሮሚያ ለሥራ ፈጣሪዎች 16 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ብድር ሰጠ

Date:

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለሥራ ፈጣሪዎች የ16 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ብድር መስጠቱን የኦሮሚያ ክልል ሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ካሣ እንደተናገሩት፤ በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የኢንተርፕርነርሺፕ ሥልጠና የወሰዱ ሲሆን ለሥራ ፈጣሪዎች 16 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ብድር ማቅረብ የተቻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ብድር ወስዶ ወደ ሥራ ከመግባት አንጻር ማኅበረሰቡ ፍራቻ እንደነበረበት አንስተው፤ ይህም በ2016 በጀት ዓመት የቀረበው ብድር 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ብቻ መሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

ሥልጠናው ለአርሶ አደሩ በዘመናዊ መልክ የግብርና ሥራን መሥራት የሚያስችል፤ በአምራች ኢንዱስትሪው የተሰማሩ ምርታቸውን ከሀገር ውስጥ ገበያ ባለፈ ለውጭ የሚያቀርቡበትን እና በስፋት ተኪ ምርት ማምረት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማስቻል ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በተሰጠው ሥልጠና እና የኅብረተሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጫ በኋላ ወደ ሥራ መግባት እንዲችሉ የብድር አገልግሎት ተመቻችቶላቸዋል ብለዋል፡፡

የተሰጡ ሥልጠናዎች ውጤታማ በመሆናቸው በ2017 በጀት ዓመት በ182 ሺህ ኢንተርፕራይዝ፤ ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተደራጅተው ወደ ሥራ መሰማራታቸውን ተገልጿል ።

NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...