የሶማሊላንድ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ፕሬዝደንታዊ ምርጫውን አሸነፉ

Date:

የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ተቃዋሚ መሪ ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን በዛሬው እለት ይፋ ማድረጉን ኤፒ ዘግቧል።

የዋና ተቃዋሚው ዋዳኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሀመድ አብዱላሂ ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ማግኘት ችለዋል።

ለሰባት አመታት ሶማሊላንድን የመሩት የቀድሞው ገዥ ፓርቲ ኩልምዬ መሪ ሙሴ ቢሂ አብዲ 30 በመቶ ድምጽ በማግኘት ሁለተኛ ሆነዋል።

ምርጫው በበጀት እጥረት እና በሌሎች ምክንያቶች ከ2022 ወዲህ ለሁለት ጊዜ መራዘሙ ይታወሳል።

 ግጭት እየተካሄደ በነበረበት በ1991 ከሶማሊያ የተገነጠለችው ራስ ገዟ ሶማሊላንድ አለምአቀፍ እውቅና ባይኖራትም የራሷ መንግስት፣ መገበያያ ገንዝብ እና የራሷ የጸጥታ መዋቅር አላት። ሶማሊላንድ ከሶማሊያ ይልቅ ለአመታት የተረጋጋች ሆኗ ቆይታለች።

ሶማሊሊንድ ባለፈው የፈረንጆቹ አዲስ አመት ከጎረቤት ኢትዮጵያ ጋር የተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ሉአላዊነቴ ተጥሷል በምትለው ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...