አደንዛዥ ዕፅ የጫኑ መርከቦች ጥቃት

Date:

በፓሲፊክ ውቂያኖስ አደንዛዥ ዕፅ እንደጫነ የተጠረጠረ መርከብ ላይ ጥቃት በመፈፀም ሁለት ሰዎችን መግደሉን ፔንታጎን አስታውቋል።

እንደ አሜሪካ የመከላከያ ዋና ፀሀፊ ፔት ሄግሰን ገለፃ መርከቧ በአሜሪካ የስለላ ድርጅት እንደ ተደረሰባትና አደንዛዥ ዕፅ ጭናለች ተብሎ በመታመኑ ጥቃት መፈፀማቸው አስታውቀዋል።

በጥቃቱ በመርከቡ የነበሩ ሁለት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በአሜሪካ ወታደሮች ላይ የደረሰ ጉዳት ስላለመኖሩ አስታውቀዋል።

ከአውሮፓውያኑ መስከረም 2 ወዲህ አሜሪካ አደንዛዥ እፅ ጭነዋል ብላ ያመነችባቸውን ጀልባና መርከቦች ላይ ጥቃት ስትፈፅም የአሁኑን ጨምሮ ለስምንተኛ ጊዜ ሲሆን፤ በፓሲፊክ ውቂያኖስ ሲፈፀም ግን የመጀመሪያዋ ነው።

ዶናልድ ትራምፕ በአለምአቀፍ የውሀ መተላለፊያዎች የሚንቀሳቀሱ ህገወጥ መርከቦች ላይ እርምጃ የመውሰድ ህጋዊ መብት አለኝ ያሉ ሲሆን ይህንን ስልጣናቸውን ማስፉት ካሻቸው ወደ አሜሪካ ኮንግረስ እንደሚያቀኑ አስታውቀዋል።

አስተዳደራቸው ፀረ አደንዛዥ እፅ እንቅስቃሴዎችን በስፋት ለመጀመር መዘጋጀቱንም ገልፀዋል ትራምፕ።

ምክትላቸው ማርኮ ሩቢዮ በበኩላቸው በኦቫል ኦፊስ በነበራቸዎ መግለጫ መርከቦች ሲጋዩ ላለመመልከት የትኛውም ሀገር ወደ አሜሪካ አደንዛዥ እፅ መላኩን ማቆም ይገባዋል ብለዋል።

NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...