በከተማው ባሉ ሁሉም ቀበሌዎች ከዛሬ ጀምሮ መደበኛ መታወቂያ ተሰርዟል

Date:

የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር የቀበሌ መታወቂያ እንዳይሰጥና እንዲሰረዝ እንዲሁም በከተማው ማንኛውም አገልግሎት የሚሰጠው በብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ብቻ መሆኑን አስታውቋል።

‎ከዛሬ ጀምሮ ሁሉም ሰው በብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ብቻ እንዲጠቀምና በከተማው በሁሉም ቀበሌያት መደበኛ መታወቂያ እንዳይሰጥና እንዲሰረዝ ነው አስተዳደር ምክር ቤቱ የወሰነው።

ከተማ አስተዳደሩ በከተማው የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ተግባራትና ወንጀሎች ለመከላከል በማሰብ ለማንኛውም ዓይነት አገልግሎቶች ህብረተሰቡ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ብቻ እንዲጠቀም አሳስቧል።

‎በከተማው ባሉ ሁሉም ቀበሌዎች ከዛሬ ጀምሮ መደበኛ መታወቂያ እንደማይሰጥና እንደተሰረዘ ነው የተገለጸው።

ነዋሪዎች እንዲሁም በከተማው የሚንቀሳቀሱ ማንኛውም ግለሰብ ከዚህ በኃላ ምንም ዓይነት የቀበሌ መታወቂያ መጠቀም እንደማይቻልም አጽንኦት ሰጥቶ ገልጿል።

‎በመሆኑም የመደበኛ መታወቂያ የሰጠ እንዲሁም በመታወቂያው የተጠቀመ ግለሰብ በህግ እንደሚጠየቅም ነው ያሳሰበው።

መረጃው የከተማ አስተዳደሩ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።

@TikvahethMagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...