ሀማስ ያልተቀበለው ውሳኔ

Date:


የአውሮፓ ህብረት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የጋዛን ግጭት ለማስቆም ያሳለፈውን ውሳኔ እንደተቀበለው አስታወቀ ።

የጋዛን ግጭት እስከወዲያኛው ይፈታል ተብሎ የታመነበትን ባለ20 ነጥብ የሰላም ዕቅድ ለቀጣናው አጠቃላይ ገፅታ አስፈላጊ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል ።

የአውሮፓ ህብረት ቃል አቀባይ አኑዋር ኤል አኖኒ በብራሰልስ በሰጡት መግለጫ ፣ የተመድ ውሳኔ ሰብዓዊ እርዳታ በሚገባበት ፣የመልሶ ግንባታ በሚካሄድበት እና ተቋማዊ እድሳት በሚከናወንበት ሁኔታ መምከሩ እና ውሳኔ ላይ መድረሱ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉ አወድሰውታል ።

ህብረቱ ከተመድ እና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመሆን በጋዛ አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ይሰራል ብለዋል ቃል አቀባዩ ።

ምን እንኳ የፀጥታው ምክር ቤት በጋዛ የሰላም እና ደህንነት አስከባሪ ሀይሎች እንደሚገቡ ከውሳኔ ቢደርስም ሀማስ ግን ውሳኔውን አልተቀበለውም ተብሏል ።

ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...