ጤና ሚኒስቴር አንድ ተጨማሪ ሰው በማርበርግ ቫይረስ በሽታ መያዙን አስታወቀ

Date:

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #ጂንካ ከተማ በተከሰተው ማርበርግ ቫይረስ አንድ ተጨማሪ ሰው መያዙን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ፣ ትላንት ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ዘጠኝ የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ አንድ ሰው በቫይረሱ መያዙን ማረጋገጡን ገልጿል።

በዚህም አጠቃላይ በማርበርግ ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 4 ደርሷል ብሏል። የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የቫይረሱ ምልክት ታይቶባቸው ህይወታቸው ካለፈ ስድስት ሰዎች መካከል ሦስቱ ሰዎች የሞቱት በቫይረሱ መሆኑን ህዳር 8 ቀን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመከላከል እና በመቆጣጠር ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ የ #አሜሪካ መንግስት ዝግጁ መሆኑን አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ገልጸዋል።

አምባሳደሩ ይህን የገለጹት፣ በኢትዮጵያ በተከሰተው የማርበርግ የቫይረስ በሽታ አጠቃላይ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት ዙሪያ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጋር ትላንት በተወያዩበት ወቅት ነው።

ዶ/ር መቅደስ የበሽታውን የላብራቶሪ ምርመራ፣ ከታማሚዎች ጋር የነበሩ ንክኪዎች ክትትል፣ የአደጋ ዝግጁነት እና የማህበረሰብ ተሳትፎን ጨምሮ አስቀድመው የተተገበሩ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎችን አብራርተዋል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...