እስራኤል የኢትዮጵያን የባህር በር የማግኘት ጥረት ሙሉ ለሙሉ ትደግፋለች

Date:

ኢትዮጵያ ለኢኮኖሚዋ፣ ሉአላዊነቷና ደህንነቷ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት እስራኤል ታምናለች ያሉት በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራም ንጉሤ ፤ እስራኤልም ኢትዮጵያ ለምታደርገው ጥረት በዲፕሎማሲና በሰላማዊ መንገድ ከኢትዮጵያ ጎን እንደምትቆም ተናግረዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው ያሉት አምባሳደር አቭራም፤ ሁለቱ ሃገራት ጥንታዊና ልዩ የሆነ የብዙ አመታት የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላቸው መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ በዚህኛው ዘመንም ሁለቱ ሀገራት የሚተባበሩና የሚረዳዱ ናቸው ብለዋል፡፡

“በአለም አቀፍ መድረክም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጭምር እስራኤል ኢትዮጵያን ትደግፋለች፤ ኢትዮጵያም እስራኤልን ትደግፋለች፤ ይህ መደጋገፍ ግን በኢኮኖሚውም በጤናውም በግብርናውም ጭምር ነው” ሲሉ አክለዋል፡፡

የእስራኤል ፓርላማ አባል የሆኑት ዶ/ር ጸጋ ፋንታሁን በተመሳሳይ፤ “ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማግኘት መብቷ የተጠበቀ ነው” ብለዋል፡፡

በእስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር ተስፋዬ ይታይህ በበኩላቸው፤ “በእስራኤል በኩል ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋን የመቃወም አዝማሚያ አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡

“ኢትዮጵያ እንደገና መልሳ ወደ ቀይ ባሕር ጠረፍ ብትመጣ አንደኛ ወዳጅ ሀገር ናት፤ በተጨማሪም እስራኤል ኢትዮጵያን መግቢያ በር አድርጋ ስለምትመለከታት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር እንድታግዛት ትፈልጋለች” ብለዋል።

ኢትዮ ኤፍኤም-

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...