5 የገበታ ጨዉ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ተነገረ

Date:

የጥንቃቄ #መልክት

የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች በሚመለከተው አካል የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳይሰጣቸውና ጥራትና ደረጃቸው ሳይረጋገጥ ገበያ ላይ በመገኘታቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለስልጣኑ አሳሰበ፡፡

አዲስ አበባ፡ መጋቢት 4፣2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በቅርቡ ገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር አምስት የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳያገኙ ምልክቱን ለጥፈው ገበያ ላይ ውለው ተገኝተዋል፤በመሆኑም እነዚህ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለሰልጣኑ ያሳስባል፡፡

ምስላቸው እና ዝርዝራቸው ከዚህ በታች የተቀመጡ የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ ደረጃ ምልክቱን የመጠቀም ፈቃድ ያላገኙና ጥራት እና ደህንነታቸው ያልተረጋገጠ በመሆናቸው ያሳውቃል፡፡

  1. ሊኑ የገበታ ጨው /LINU IODIZED SALT /፣
  2. ታሪክ የገበታ ጨው /TARIK TABLE SALT /፣
  3. SALT BAY፣
  4. ሺማ አዮዳይዝድ ጨው /SHIMA IODIZED SALT/
  5. እና ጂ.ኤም ኤዳይዝድ ጨው /G.M Iodized salt/ በሚባል የምርት ስም የሚጠሩ ናቸው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...