“መንግሥት  ለትግራይ ክልል በቅርቡ በጀት ለመልቀቅ ተስማምቷል”

Date:

የትግራይ  ክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የፌደራል  መንግሥት በቅርቡ  ለክልሉ  በጀት ለመልቀቅ መስማማቱን ገለጸ፡፡

  ውሳኔው በጊዜያዊ አስተዳደሩ ልዑክና በፌዴራል መንግሥት ባለስልጣናት መካከል ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ከተካሄደው ውይይት በኋላ መተላለፉን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ አስታውቀዋል፡፡

ውይይቱ የትግራይን የንግድ ማኀበረሰብ እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮችን፤ በተለይም የባንክ ብድርና የወለድ ክፍያዎችን እንደዳሰሰ በመጠቆም፤ የተደረሱት ስምምነቶች ወደ ግጭት ላለመመለስ የሚደረገው ሰፊ ጥረት አካል እንደሆኑ ገልጸዋል።

“የፌዴራል መንግሥት የውስጥ ፖለቲካ ጉዳዮችን በውይይትና በመግባባት ለመፍታት ፈቃደኝነቱን አሳይቷል” ሲሉ ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ውጥረቱን የበለጠ ሊያባብሱ በሚችሉ ድርጊቶች ውስጥ እንደማይሳተፍ ለፌዴራል ባለሥልጣናት ማረጋገጫ መስጠቱን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምግባረ-መልካሙ ኢትዮጵያዊ

ስለሺ መንገሻ - ከ1934 እስከ 2018 ዓ.ም ሠሎሞን ለማ ገመቹ. ግዮን...

ትራምፕ ለኔታንያሁ ማስጠንቀቂያ ሰጡ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ...

ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ...

የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ከዓመታዊ የትርፍ 90 በመቶውን እንዲያከፋፍሉ ሊደረግ ነው

የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ተብለው የሚቋቋሙ ፈንዶች ከዓመት ትርፋቸው ቢያንስ...