ኢትዮጵያ በዙሪያዋ ያሉ ወደቦችን በባቡር ለማገናኘት የ5 ሺህ ኪሎ ሜትር መስመር ጥናት ማጠናቀቋ ተሰማ
ኢትዮጵያ በርበራ፣ ሞምባሳ፣ ጂቡቲና ፖርት ሱዳንን ጨምሮ በዙሪያዋ ያሉ ሁሉንም ወደቦች በባቡር መስመር ለማገናኘት የ5 ሺህ ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር ጥናት ማጠናቀቋን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርዖ ሐሰን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በዙሪያዋ ያሉ ወደቦችን በባቡር ለማገናኘት ሰፊ ዕቅድ ይዛ እየሠራች ትገኛለች።
ጥናቱ የተጠናቀቀው የ5 ሺህ ኪሎ ሜትር መስመርም ይህንን የትስስር ዕቅድ ለማሳካት ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።
የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ባለሙያዎች ሥራውን ከተረከቡ በኋላ የጥገና አቅማቸውን እያሳደጉ መሆኑን የገለጹት አቶ በርዖ፤ ወደቦችን ለማገናኘት የተጠኑ አዳዲስ የባቡር መስመሮችም ወደ ተግባር እንዲገቡ አስፈላጊው ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
