2 ነጥብ 6 ሚሊየን ዓመታትን ያስቆጠረ የሰው ልጅ ዝርያ በአፋር ክልል ተገኘ

Date:

2 ነጥብ 6 ሚሊየን ዓመታትን ያስቆጠረ እና ፓራንትሮፕስ የሚል ስያሜ ያለው የሰው ልጅ ዝርያ በአፋር ክልል ሚሌ ሎጊያ በተባለ ስፍራ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር በሰጡት መግለጫ፥ ባለስልጣኑ ከሚያከናውናቸው ሥራዎች አንዱ የሰው ልጅ ቅሪት አካላት ላይ ምርምር ማድረግ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ተመራማሪዎች ከውጭ ሀገራ ተመራማሪዎች ጋር በመሆን ባደረጉት ጥናትና ምርምር አትዮጵያ የሰው ዘር መገኛነቷን በዓለም መድረክ አስተዋውቀዋል ነው ያሉት።

በዛሬው ዕለትም ከዚህ በፊት ያልታዬ የሰው ልጅ ዝርያ በአሜሪካ የችካጎ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ በሆኑት ዘረሰናይ ዓለምሰገድ (ፕ/ር) በተመራ ልዑክ መገኘቱን ተናግረዋል።

ግኝቱ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን እና ለአንተሮፖሎጂ ምርምር ኢትዮጵያ እና የአፋር ክልል ተመራጭ መሆናቸውን የበለጠ የሚያረጋግጥ መሆኑን አመላክተዋል።

ግኝቱ በዓለም ላይ ታዋቂ በሆነው ኔቸር መጽሔት ላይ በዛሬው ዕለት እንደሚታተም ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...