የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድህረ ክፍያ

Date:

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው የፍጆታ ሂሳባቸውን ማወቅ የሚችሉበትን አሰራር በሙከራ ደረጃ አስጀምሯል፡፡

የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አንዋር አብራር እንዳሉት÷ የተጀመረው አሰራር ከድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቅረፍ ያስችላል፡፡

ከደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ደንበኞቹ ባሉበት ሆነው የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም የቆጣሪ ንባባቸውን የሚያስገቡበት የቴሌግራም ቻትቦት የሙከራ ትግበራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡

የሙከራ ትግበራው ከ16 ሺህ በላይ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ባሉበት የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ቁጥር አራት የአገልግሎት መስጫ ማዕከል ላይ ብቻ ተጀምሯል ነው ያሉት፡፡

በዚህም ከየካቲት 13 ቀን እስከ የካቲት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ደንበኞች የፍጆታ ንባባቸውን በቀላሉ በቤታቸው ሆነው በ @eeuchatbot ለተቋሙ እንዲልኩ ጥሪ መቅረቡን ጠቁመዋል፡፡

የዲጂታል አሰራሩ ለደንበኞች በቀላሉ ተደራሽ ለመሆን፣ የፍጆታ ሂሳብን በወቅቱ ለመፈጸም፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም ጊዜና ወጪን ለመቆጠብ ያስችላል ማለታቸውን ፋና ዘግቧል፡፡

በሙከራ ደረጃ የተጀመረው አሰራር ያሉበትን ክፍተቶች እና ጥንካሬዎች በመለየት በቀጣይ በሌሎች ሪጅኖች እና የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለማስፋት መታቀዱንም ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...