የእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ለእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ የመላው ጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየምን አስጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ለሀገር ሉዓላዊነትና ለነፃነት ዋጋ የከፈሉ ጀግኖች ታሪክ ለፕሬዚዳንቱ ተብራርቶላቸዋል።

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባተላለፉት መልዕክት፤ ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ለነበራቸው ቆይታ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አያይዘውም ፕሬዚዳንቱ በምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚኖራቸው ቆይታ ፍሬያማና ስኬታማ እንዲሆን በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ይህ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር እንደሆነም ታምኖበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...