አል ዐይን አማርኛ ሥራ ሊያቆም ነው

Date:

ባለቤትነቱ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት የኾነው አል ዐይን አማርኛ የበይነ መረብ የዜና ማሠራጫ ሥራ ሊያቆም ነው ፡፡

የዜና ማሠራጫው በአማርኛ ቋንቋ ዜናዎችንና ዘገባዎችን የሚያዘጋጁ የኢትዮጵያ ዘጋቢዎቹን የቅጥር ውል አቋርጧል ፡፡

ተቋሙ የሠራተኞቹን ውል ያቋረጠው፣ የአማርኛ ዜና አገልግሎቱን አቁሞ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ለመውጣት በማሰቡ መኾኑን ተዘግቧል፡፡

ዘጋቢዎቹ ሥራቸውን እየሠሩ ባሉበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቂያ ሳይደርሳቸው፣ በድንገት የሥራ ውላቸው መቋረጡን የሚያመላክት መልዕክት በኢሜይል እንደደረሳቸው ዋዜማ ሰምታለች፡፡

ከአምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የዜና አገልግሎት የጀመረው አል ዐይን አማርኛ ከትናት በስትያ ጀምሮ ዜናዎችን አላሠራጨም፡፡ የዜና ድረረገጹ በዋናነት ትኩረቱን በመካከለኛው ምሥራቅ ላይ አድርጎ የአገር ውስጥና ዓለማቀፍ ዜናዎችን በአማርኛ ቋንቋ ለኢትዮጵያዊን አንባቢዎች ሲያቀርብ ነበር ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...