ብዕርና ባሩድ በአሜሪካ በካናዳና በአውሮፓ ገበያ ላይ ዋለ

Date:

በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት የተመረቀው የአንዱዓለም አራጌ አዲስ መጽሐፍ ብዕርና ባሩድ በአሜሪካ ታትሞ በተለያዩ ከተሞች ለገበያ ቀርቧል።

ብዕርና ባሩድ በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሲልቨር ስፕሪንግ፣ በቨርጂኒያ፣ በሂውስተን፣ በዴንቨር፣ በዳላስ፣ በኦክላንድና ሳንሆዜ በሽያጭ ላይ ይገኛል።

በተጨማሪም በካናዳ ቶሮንቶ ለአንባቢዎች ደርሷል።

በአውሮፓ ደግሞ በጀርመን ፍራንክፈርትና በርሊን፣ በስዊዘርላንድ፣ በሆላንድ አምስተርዳም እንዲሁም በስዊድን ስቶክሆልም ለአንባቢዎች መቅረቡ ታውቋል።

ይህ አዲስ መጽሐፍ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሰንሰለት በጥልቀት የሚፈትሽና ብዙ የሚያወያዩ ቁምነገሮችን የያዘ ሲሆን፣ ለሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄዎችን የሚያመለክት ድንቅ ሥራ መሆኑ ተገልጿል።

መጽሐፉን በኢትዮጵያ ገበያ ለማቅረብ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚገኙ የአንላይን ተጠቃሚዎችም በቅርቡ በአማዞን ላይ እንደሚጫን ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...